July 16, 2026
ዜና (News)
26
የሰ/ት/ቤቱ የ3 ዓመት የአገልግሎት ሪፖርት በጠቅላላ ጉባኤው ጸደቀ።
የሰ/ት/ቤቱ የ3 ዓመት የአገልግሎት ሪፖርት በጠቅላላ ጉባኤው ጸደቀ።
የደ/ነ/ቅ/ዮሐንስ እና መ/ጎ/ቅ/ማርያም ቤ/ክ የፍቁረ እግዚእ ሰ/ት/ቤት በ2016 የተመረጠው ሥራ አመራር 3ኛ ዓመት 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ያለፉትን 3 ዓመት የአገልግሎት ሪፖርት የሰ/ት/ቤቱ አባላት በተገኙበት በሰንበት ት/ቤቱ አዳራሽ በዛሬው ዕለት ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርቧል ።
በጠቅላላ ጉባኤው ላይ በሰንበት ት/ቤቱ ባለፉት 3 ዓመት የተከናወኑ አገልግሎቶችን በተመለከተ ሪፖርት በሰንበት ት/ቤቱ ሰብሳቢ ዳግም ጌታቸው ቀርቧል።
በአገልግሎት ሪፖርት ዙሪያ የሰንበት ት/ቤቱ አባላት የተለያዩ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመቀጠል የክፍላት ተጠሪዎች ለጠቅላላ ጉባኤው ለ3 ዓመታት በአገልግሎት አብረዋቸው ለደከሙ ለሰንበት ት/ቤቱ አባላት የምስጋና እና የይቅርታ መልእክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻ የሰንበት ት/ቤቱ ጽ/ቤት አመራሮች ለአገልግሎቱ መሳካት የተባበሩ የአገልግሎት ሒደት በጥሩ መንገድ እንዲሳካ ላደረጉ አካላት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን በአገልግሎት ሂደት የተከፉ አባላት ካሉ አመራሩን በመወከል የይቅርታ መልእክት የሰንበት ት/ቤቱ አመራር ጽጌረዳ ገ/ዮሐንስ አስተላልፋ በአንድነት በምስጋና መዝሙር መርሐ ግብሩ በጸሎት ተፈጽሟል ።
❤1🙏1